Antsokya

Tuesday, June 25, 2013

የኢትዮጵያ የአበባ ምርት በአፍጋኒስታን ገበያ አገኘ እንዴ?

! የአየር መንገዳችን የጭነት ጥያራዎች በግንቦት እና በያዝነው ሰኔ ወራት ወደ አፍጋኒስታን ደፋ ቀና ሲሉ ታይተዋል። (Flight Radar24.com ድረ-ገጽን ይመልከቱ)
ሐቅ! አየር መንገዱ ስድስት የጭነት ጥያራዎችን አሰማርቶ በቋሚ መልክ ወደ አውሮፓ፤ መካከለኛው ምሥራቅ እና እስያ ሸቀጣ ሸቀጥ ያመላልሳል። ኾኖም አፍጋኒስታን በቋሚነት ከሚበርባቸው አገሮች መኻል ያልተመዘገበች ከመሆኗም ባሻገር በጦርነት ከተዘፈቀች አገር ጋር ምን ዓይነት ንግድ ተጀመሮ ይሆን የሚያስብሉ ሰባት በረራዎች ቀልቤን ሊስቡት ችለዋል።
ሐቅ! አፍጋኖቹ ያለፉትን ሦስት-አሥርት ያህል ዓመታት ያሳለፉት እርስ በርስ በመፋጀት፤ በመፈራረቅ አገራቸውን የያዙባቸውን የሁለቱን ኃያላን መንግሥታት ወራሪ ሠራዊቶች በመከላከል እና በመኻሉም አክራሪ-ሃይማኖተኝነትን መርኅ በማድረግ ነው። የአገራቸው መልክዓ-ምድር እንደ ኢትዮጵያ ተራራማ ከመኾኑም ባሻገር የገጠሩ ዜጋ አኗኗር የኛውኑ ገጠሬ ጋር ይመሳሰላል። በጎቻቸው እንኳ በላት ምትክ ቂጣሞች ይሁኑ እንጂ የኛውኑ የአዳል ሙክት ነው የሚመስሉት። ግን ከኋላቸው ሲያስጠሉሉሉሉሉሉ!
afghanistan sheeps and Ethiopiaእንግዲህ ለዚህ መጣጥፍ መነሻ የሆነኝ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ልዩ የጭነት በረራዎች በግንቦት ወር አራት (የመጀመሪያው በረራ ግንቦት 14 ቀን 2005 ዓ/ም ነበር) ጊዜ
እና በያዝነው የሰኔ ወር ደግሞ ሦስት ተመሳሳይ በረራዎች (ወሩ ገና ስላላለቀ ሌሎችም ሊኖሩ ይችላሉ!) የአሜሪካ ሠራዊት የሚጠቀምበትን የካንዳሃር ጥያራ ጣቢያ ሲጠቀሙ መገንዘቤ ነው። ለአሜሪካ ሠራዊት የቀንድ ከብት ጭነው ይኾን እንዴ? አይ ግዴላችሁም አበባ መሆን አለበት! ግን አንዱ በረራ ከሊዬዥ ቤልጂግ ተነስቶ ካንዳሃር ካረፈ በኋላ መልሱን በሆንግ ኮንግ በኩል ሲያደርግ ነዋ የታየው። ስለዚህ ጭነቱ አበባ ቢሆን ኖሮ ከአዲስ አበባ፣ ሊዬዥ፤ ከሊዬዥ ዱባይ፤ ከዱባይ ካንዳሃር እስከሚገባ አበባው የሚጠወልግ እና የኪሣራ ኪሣራ ነው የሚሆነው።
ወይ ከአፍጋኒስታን እነኛን የአዳል ሙክት የሚመስሉትን በጎች መንግሥታችን ሸምቶልን ይሆናላ! አይ፣ ወይ የሁዳዴ ወይ የረመዳን ጾም መፍቻ ወቅት ቢሆን ኖሮ በግ ተሸምቶልን ነው ለማለት ይቻል ይሆን ነበር። በግንቦትና በሰኔ ወራት ግን አይመስልም። እሺ! አየር መንገዳችን ሰራተኞቹን በጭነት አውሮፕላን እያጓጓዘ የዓመት እረፍታችውን በራሱ ወጭ አፍጋኒስታን ወስዶ ማዝናናት ጀመረ እንዴ ? እንደዚያ ከሆነ ጎረቤት አገር ኬንያ እየወሰደ ቢያዝናናቸው ወጭው አይቀልለትም ኖሯል ? ደግሞስ ጦርነት እሚካሄድበት አገር ወስዶ ለአደጋ ቢያጋልጣቸው የዋስትና ሽፋኑ አይከሽፍበትም ? አይ ምክንያቱ ይኼም ሊሆን አይችልም። በነገራችን ላይ ምንም ጭኖ ወይም ለመጫን ይሁን አፍጋኒስታን የሄደው በሽብር መኻል ጥያራው የተንኮል አደጋ ቢደርስበት የአየር መንገዱ ዋስትና ይሸፍነው ይኾን?
Ethiopian Airlines, cargo planes in Afghanistan ታዲያ በስድስት ጠብድያ የጭነት ጥያራዎች የተጓጓዘው ምንድነው እንበል ? ምነው ዴሞክራሲ እና ግልጽነት በሰፈነበት አገር ተወልደን በሆነ ኖሮ? አየር መንገዳችን በየአንዳንዱ በረራው ከየት ተነስቶ ወዴት፤ ምን ጭኖ እንደሚንቀሳቀስ፤ በጥያራው ግዥ ያባከንነው ገንዘባችን ለኛው ትርፍ እየተሰራበት መሆን አለመሆኑን እና የመሳሰሉትን ጥያቄዎቻችንን የመጠየቅ ብቻ ሳይሆን አጥጋቢ መልስ የማግኘት መብትም ይኖረን ነበር።
ቆይ ቆይ! የአሜሪካ ሠራዊት ከአፍጋኒስታን የመውጣት ዝግጅቱን እያጧጧፈ ነው የሚል ትንተና አንብቤ የለም እንዴ? አዎ! ሠራዊቱ ቁሳቁሱን አጠቃሎ እ.አ.አ. 1914 መጨረሻ በፊት እንዲወጣ በተወሰነው መሠረት የጊዜ ገደቡ ከመድረሱ በፊት ለማገባደድ ዝግጅቱን እያመቻቸ ይገኛል። የተከማቸውን የጦር መሣሪያ በያይነቱ፤ የመመላለሻ መኪናዎች፤ የተቀበረም ኾነ በሽምጥ የተነጣጠረ ፈንጂ መቋቋም የሚችሉ ተንቀሳቃሾችን (በእንግሊዝኛው Mine-Resistant Ambush Protected (MRAP) vehicles ይሏቸዋል) ማንሳት ይጠይቃል። ታዲያ ዕድሜ ለኅብረ-መረብ (ኢንተርኔት)፤ ሰሞኑን ያነበብኳቸው መጣጥፎች እንደሚገልጹት፣ ከአሜሪካው ዜጋና የሕዝብ ተወካዮች ሸንጎ የተደበቀ መፍትሄ ቢሆንም የሠራዊቱ ዓለቆች ከሃያ በመቶ (በግምት ሰባት ቢሊዮን ዶላር) የሚኾነውን የጦር መሣሪያና ተሽከርካሪዎች፤ የመገናኛ ቁሳ-ቁሶችና ንብረት — አላስፈላጊ ወይም ወደአሜሪካ የማጓጓዣው ወጭ ይከብዳል የሚል ውሳኔ ላይ ደርሰዋል — ከቻሉ ወዳጅ አገራት በራሳቸው ወጭ አስነስተው መውሰድ እንደሚችሉ፤ በዚህ ዓይነት ያልተነሳውን (ብልጫውን) ደግሞ እዚያው አፍጋኒስታን ውስጥ በመሰባበር ማውደም ላይ መኾናቸው ተዘግቧል።
ለምሣሌ የአሜሪካው ሠራዊት በአፍጋኒስታን ካሰማራቸው አሥራ-አንድ ሺ (አሥራ-አንድ ሺ) ኤም. አር. ኤ. ፒ. መኪናዎች (እያንዳንዳቸው አንድ ሚሊዮን ብር ነው ያወጡት!) ሁለት ሺዎቹን መልሶ እንደማይወስድ (ከነኚህም አብዛኛዎቹ ማጓጓዣቸውን አመቻችቶ የሚወስድ ወዳጅ አገር ስለሌለ እዚያው እንደሚሰባበሩ) ቀሪዎቹ ዘጠኝ ሺ መኪናዎች ደግሞ ወደአሜሪካ እና በየአገሩ ወደተሠማሩት የአሜሪካ ሠራዊት እዞች (ይሄም ኢትዮጵያን ሊመለከት ይችላል) እንደሚላኩ የፔንታጎን ቃል አቀባዮች መግለጻቸውን አንብቤያለሁ። ጉድ እኮ ነው!
ታዲያ ወያኔ ምኑ ሞኝ ነው! የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጭነት ጥያራዎችን አሰማርቶ በነፃ የሚገኘውን መሣሪያ እና ኤም. አር. ኤ. ፒ. መኪናዎች ለማንሳት ነዋ ወደካንዳሃር ያዘዛቸው! በርሮበት ወደማያውቀው ጥያራ ጣቢያ፤ የኔ ብጤውን ተከታታይ ለማደናበር ሰባቱንም በረራዎች ከካንዳሃር በቀጥታ ወደሆንግ ኮንግ በማብረር (መሠረታዊ የጭነት በረራ መሥመር ባይሆንም እንኳ ሆንክ ኮንግ ከካንዳሃር የተሻለ ታማኝነት ይኖረዋል) ያለጥርጥር መሣሪያውን በምሥጢር እያጓጓዙ ነው ወደሚለው ድምዳሜ በበኩሌ የደረስኩ መሆኔ ይሰመርልኝ።
መችም “የስጦታ ፈረስ ጥርሱ አይገለጥም” የሚባለው የአባቶች ብሒል አይታዘበኝና፤ ገዢው የወያኔ ኃይል ዘጠና ዘጠኝ ነጥብ ስድስት ከመቶውን ወንበር በሚቆጣጠርበት “የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት” (ድንቄም የሕዝብ ውከላ እቴ!) ያሉት አንድዬው ተቃዋሚ አቶ ግርማ ሰይፉ እውነታውን ተገንዝበው ጥያቄ ቢያቀርቡም እንኳን ምናልባት ከአቶ መለስ የለመድነውን የትዕቢት ዘለፋ ከማትረፍ በቀር እውነት ያለበትን ጎራ እንኳ አቅጣጫ ይጠቆማሉ ብሎ ማሰብ ከንቱ ነው። እንኳን የአሜሪካኖቹ ትርፍራፊ በኛው ላይ ሊነጣጠር የታሰበ ሊሆን እንደሚችል ሊነገረን ቀርቶ ለምጽዋቱ እንኳን እንደባህላችን “እግዚአብሔር ይስጥልን” ለማለት አይፈቀድልንም። ታዲያ አቶ ኦባንግ ሐሙስ ዕለት በአሜሪካው ኮንግረስ ላይ “እራሳችንን እኛው ነፃ እናወጣለን። እናንተ ግን የመንገድ እንቅፋት አትሁኑብን!” ያሉዋቸውን በአንድ ፊት እናዳምጣለን የሚሉን አሜሪካኖች በጎን ወያኔን በምስጢር እስከቅንድቡ ድረስ እያስታጠቁት ነው።
እንግዲህ ለተጋለጡት በረራዎች የወያኔ አካላትም ሆኑ ደጋፊዎቻቸው ምክንያት አድርገው ሊያቀርቡ የሚችሏቸውን መልሶች በመንደርደሪያዬ ላይ እንደሸፈንኳቸው ተስፋ እያደርግሁ ያልተለመደ፤ ያልተገለጸ፤ የንግድ ዓላማ ሊኖረው የማይችል እና ማደናበሪያ አቅጣጫዎችን ያካተተ ከካንዳሃር አፍጋኒስታን የሚነሱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጭነት ጥያራ በረራዎች የጦር መሣሪያዎችንና ወታደራዊ ቁሳ-ቁሶችን ለማንሳት ካልሆነ በቀር ሌላ ምክንያት አልታየኝም። ይልቁንስ ተቃዋሚ ቡድኖች ካሁኑ ማንሳት ያለባቸው 1ኛ) አሜሪካኖቹ በነፃ ውሰዱ ያሉትን ከፍ ያለ ዋጋ ከፈልንበት ብለው የለመዱትን ብዝበዛ እንዳያካሂዱ 2ኛ) ምስር ልትወጋን እየተነሳሳች ስለሆነ መከላከያ መሣሪያ ብለን ነው እንዳይሉ ከምስር ጋር እያካሄዱት ያለው የአፍ ጦርነት በሁለቱም በኩል የገዥ አካላቱን ዕድሜ ማራዘሚያ ስልት እንጂ ሌላ ምንም ትርጉም የሌለው መሆኑን 3ኛ) ምዕራባውያን በፊት ለፊት የዴሞክራሲ፣ የሰብአዊ መብት፣ ወዘተ
ደጋፊናተቸውን በመለፈፍ እየሸነገሉ በኋላው በር ግን እኛኑ የሚያስቀጥቀጥ ግፊታቸውን እንደማያቆሙ እንደነቃንባቸው ማሳወቅ ነው።
ምንጮች
Posted by shume worke at 5:57 AM No comments:
Email ThisBlogThis!Share to XShare to FacebookShare to Pinterest

Monday, June 10, 2013

ይድረስ,,,,ለአጼ ቴዎድሮስ



            እንካልህ  ስሞታ፣
                         እንካልህ ደብዳቤ፣
                                 ,,,የንጉርጉሮን ድቤ፣
                                   የቅኔዬን  ስደት፣
                                    የዜማዬን ብሶት፣
                                   የስትንፋሴን ቅኝት፣
                     ማይነጋ መስሎት ,,,,
                     የዛሬው ፉኖኛ፣
                     የሌሊቱ  እረኛ፣
                     ቢያነጥፍ እስር ቤት፣
                     ቢያጠጣን ግራዋ፣
                    ቢጨምቅልን ኮሶ፣
                    ቢያሰልፈን ለቅሶ፣
                    ግዜን  ተንተርሶ፣፣
                             ,,,እንካልህ ስሞታ፣
                             ዘርህ ዋግ ሲመታ፣
                             ቀና በል አንድ አፍታ፣
                             ታዘብ ይህን ግዜ፣
                              እንካልህ  ኑዛዜ፣
                              የአማራን  ትካዜ፣
                   ሲጤስ  እንደ ኲበት፣
                  ሲቃም  እንደ  ንፍሮ፣
                  ሲጫን  እንደ  በቅሎ፣
                           ከ የት መጣህ ተብሎ,,,፣፣
                                                             በሹሜ  ወርቁ


                           ከኖርዌይ
                                                   


Posted by shume worke at 12:28 AM No comments:
Email ThisBlogThis!Share to XShare to FacebookShare to Pinterest

Tuesday, June 4, 2013

የሰሞኑ የአባይ ግርግር

Home » ዜናዎች... » የሰሞኑ የአባይ ግርግር

የሰሞኑ የአባይ ግርግር

Print Friendly Version of this pagePrint Get a PDF version of this webpagePDF
እስከ ነጻነት
ሰሞኑን በማህበራዊ መገናኛዎችና የውጭ ዜና አውታሮች ጭምር ስለ አባይ ግድብ ብዙ ሲሉ ይሰማል፡  ለምን? ለምን አሁን? ምን የተለየ ነገር ተገኘ?
በመሰረቱ አባይ መገደብና ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሀብቷ የመጠቀም መብትም ግዴታም አለባት፡ እዚህ ላይ ማንም ጥያቄ ያለው አይመስለኝም፡ ጥያቄ የሚነሳው ግን በርግጥ የትግሬ ነጻ አውጭ ግንባር የሚመራው ብድን አባይን አገድባለሁ የሚለው ለኢትዮጵያ ህዝብ ጥቅም ነው ወይ? ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር መክሮና ተስማምቶ ነው ወይ? ግድቡስ ለግርጌ ተፋሰስ አገሮች ጉዳት ያመጣል ወይ የሚሉት ጥያቆዎች መመለስ አለባቸው።
ስለ አባይ ጉዳይ ዝርዝር ከመግባቴ በፊት ወያኔ ለምን በተለያየ ዘዴ ስለ አባይ እንዲነሳ ፈለገ? ግብጽስ አሁን ሰለጉዳዩ ለምን አጀንዳ አረገችው? ወዴትስ ሊያመራ ይችላል? የሚሉትን ከወያኔ ምግባርና ጸባይ ተነስቼ ያለኝን አስተያየት አጠር አርጌ ላቅርብ፡
ወያኔ ባሁኑ ሰዓት አቅጣጫ ጠፍቶት በትርምስ ላይ እንደሆነ ይታወቃል፤ የውስጥ ሽኩቻ አለበት፤ ከውጭ ጫና አለበት፤ ህዝብ ጭቆና አንገፍግፎት በቃኝ እያለ ነው፡ ይህን ሁሉ አቅጣጫ ለማስቀየር አንድ ዘዴ መፍጠር አለበት፡ የግብጹ ሙረሲም ከግብጽ ህዝብ ሙሉ ድጋፍ የለውም እና አሱም የግብጻውያንን የልብ ትርታ የሚኮረኩር ነገር ይዞ መቅረብ ይፈልጋል፡ ስለዚህ የጋራ ሴራ አየተሸረበ ሊሆን እንደሚችል አገምታለሁ፤ በዚህ ላይ የውጭ አጅ የለበትም ለማለት አልደፍርም፡ ሁኔታው እየባሰ ከሄደ ወደ ጦርነትም ሊያመሩ ይችላሉ የሚል ግምታ አለኝ፡ በተለይ ኢትዮጵያ ጦር ሃይል ውስጥ የማፈንገጥ አዝማሚያ ያሳያሉ ብለው የሚጠረጥሯቸውን ለማስፈጀት እና እግረ መንገዳቸውንም በመርዝ፤ በጥይት፤ በማፈናቀል አላልቅ ያላቸውን ያማራ ህዝብ ባይሮፕላን ለመደብደብም አይመለሱም የሚል ግምት አለኝ ይህ ደግሞ ለትግሬ ነጻ አውጭ ግንባር አዲስ ነገር አደለም እንኳን ጠላቴ የሚለውን አማራና ነጻ አወጣሃለሁ የሚለውን ህዝብም ከመጨረስ አለተመለሰም፡
1)  ነጻ አወጣሃለሁ ያሉት ህዝብ ላይ አሲረው የነለገሰ አስፋውንና መንግስቱ ሐ/ማርያምን ደደብነት ተጠቅመው ሃውዜንን በልጆቿ ደም አጨማልቀዋታል፡
2)  ከተሸነፈ ጦር ጋር አብረን አንሰራም ብለው ለልመና የዳረጉት የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የሃገር ፍቅር ስሜቱን ስለሚያውቁና ወደፊት ለሚያቅዱት አገር የማጥፋት ሴራ እንቅፋት ይሆናል ብለው ስለገመቱ ባድሜ የሚል ድራማ ደርሰውና አራግበው በመቶ ሺ የሚቆጠር ወጣት አስጨርሰው፤ ለቤተሰቦቻቸው እንኳ በውል ልጆቻቸው የት እንደወደቁና እና የት እንደሞቱ  አልነገሯቸውም፡
3)  የአሜሪካንን ጦርነትን ለመዋጋት ሶማሊያ ድርስ የተላከው ጦር ሬሳው በመቋዶሾ ጎዳናዎች ላይ ሲጎተት ስንት እንደሞተና ስንት እንደቆሰለ እንኳ አልተነገረም እንደ ርካሽ እቃ ወድቆ ቀርቷል፡
ከዚህ ሁሉ የወያኔ እርኩስ አላማና ዘር አጥፊ ወንጀለኛ ባህሪይ ተነስቼ  በወያኔ ጠባብ ዘረኛ አስተዳደር ላይ ቅሬታ ያላቸውን የጦር ሃይል አባላት ሰብሶቦ ሊማግዳቸው ይችላል የሚል ግምት ባቀርብ የተሳሳትኩ አይመስለኝም፡  ስለዚህ መጠንቀቅ ያለባቸው ጦሩ ውስጥ ያሉና በህውሃት በጥርጣሬ የሚታዩ የሰራዊቱ አባላት ሊጠነቀቁና አይናቸውን ከፍተው በንቃት ሁኔታወችን መከታተል ያለባቸው መሆኑን አስምሬበት አልፋለሁ።
ስለ አባይ ጥቂት መረጃዎች
የአባይ ወንዝ ናይልን ከሚመግቡ ሶስት ወንዞች አንዱና ዋናው ነው፤ የወንዞቹ ተፋሰስ ስፋትና የፍሰት መጠን ከታች ባለው ሰንጠረዥ ይመልከቱ
Ethiopia's Nile river
ያባይ ወንዝ ከፍተኛው የገባር ወንዝ መነሻው 4250 ሜ ከባህር ጠለል በላይ ሲሆን ሱዳን ድንበር ላይ ከባህር ጠለል በላይ ያለው ከፍታ 490 ሜ ነው፡ (የ3760 ሜትር ልዪነት ማለት ነው)
አባይ ተፋስስ ከፍተኛ የሃይል ማመንጨትና የመስኖ ልማት አቅም ያለው መሆኑን በተፋሰሱ ላይ የተደረጉ ጥናቶች የሚያሳዩ ሲሆን በነዚህ ጥናቶች መሰረት አባይ ተፋሰስ ውስጥ በመስኖ ሊለማ የሚችል እስከ 700,000 ሄክታር የሚደርስ የመሬት ሰፋትና ከፍተኛ ሃይል ማመንጨት ሊመረትባቸው የሚችሉ አራት የግድብ ቦታዎች የገኛሉ (ካርታውን ይመልከቱ)
Ethiopian proposed hydroelectric dams
ለመስኖ ልማት አመቺ የሆነው መሬት የሚገኘው ከመንዳያ ግድብ ግርጌ ጀምሮ እስከ ሱዳን ጠረፍ ድረስ ነው፡
አባይና ደለል
ሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ ሊገነዘበው የሚገባው ነገር፡  አባይ ወንዝ ባማካይ ባመት 320 ሚሊየን ቶን ደለል ከኢትዮጵያ ኮረብታዎች ሸርሽሮና ተሸክሞ አሰዋን ግድበ መዳረሻ ላይ ይዘረግፈዋል፡ ይህም የግድቡን ውሃ የመቋጠር አቅም ይቀንሳል፡ ሊለማ የሚችለው መሬት በደለል ይሸፈናል፤ ደለሉ የውሃ መጥለፊያ ቦዮችን ይደፍናል እናም ሱዳንና ግብጽን በተለይ ሱዳንን ከፍተኛ ወጭ ያስወጣቸዋል፡ ይህ ትልቅ ችግር የሱዳንና የግብጽ የውሃ ባለሙያዎችን እንቅልፍ የነሳ ጉዳይ በመሆኑን በብዙ አለም አቀፍ መድረኮች ሲያቀርቡትና ይህንኑ ለማስቆም ኢትዮጵያ ውስጥ በተለይም አባይ ተፋስስ ውስጥ ከፍተኛ የጎርፍን መሽርሸር መከላከያ ሰራ መሰራት እንዳለበት ይመክራሉ፡ (Ahemed, 2007; Betrie  et al., 2010.)  ያቀረቡትን መመልከት ይቻላል፡
የተወራለት የአባይ ግድብ
1) ግድቡ የኢትዮጵያን ህዝብ ሊጠቅም የሚችልና የምግብ ፍላጎት በፍተኛ ደረጃ ሊቀርፍ የሚችለው የመስኖ ልማት አላካተተም
2) ወደ መሃል ሃገር ቀረብ ያሉትንና ለመስኖ ልማት ሊውሉ የሚችሉ ግድቦችን ዘሎ ድንበር ላይ መገደብ ለምን እንደተመረጠና ጠቀሜታውን የሚያረጋግጥ ምንም መረጃ ለህዘብ አልተገለጸም፡ በመስኖ የመጠቀም መብቷንም እስከወዲያኛው የዘጋ ታላቅ ሴራና አገር ክህደት ወንጀል ነው፡
3) ግድቡ የሚያመርተው የመብራት ሃይል ብቻ ነው፡ ከልምድ እንደሚታወቀው ደግሞ የውሃ ሃብት ፐሮጀክቶች ዘርፈ ብዙ እስካልሆኑ ድረስ አትራፊ እንደማይሆኑ ይታወቃል፡ ስለዚህ የአባይ ግድብ በየአመቱ ወደግድቡ የሚገባው 320 ሚሊየን ቶን ደለል ሞልቶት የግደቡ እድሜ አስኪያልቅ ድረስ እንኳን አትራፊ ሊሆን የሚገነባበትን ወጪ ለመመለሱም በእርግጠኝነት መናገር አይቻልም፤ ከህዝብም የተደበቀ የወያኔ ሚስጥር ብቻ ነው፡
4) የተፋሰሱን ጎርፍ ሽርሸራ ለመከላከል ወይም ለመቀነስ የተደረገ የተፋሰስ ልማት ስለመደረጉ ምንም የሚታወቅ ነገር የለም፡
5) ውሃው የሚተኛበት መሬት እስከመጨረሻው ከጥቅም ውጭ የሚሆን ነው፡ ደለሉ የሚከማችበት ቦታም እንደዚሁ፡ ይህን በተመለከት የምጣኔ ጥናትና አካባቢ ሁኔታ ጥናት(economic analyses, environmental impact assessment) ስለመደረጉና አዋጭ ስለመሆኑ ምንም የሚታወቅ ምንም ነገር የለም፡
6) ግደቡ ከኢትዮጵያ ይልቅ የሚጠቅመው የግርጌ ተፋስስ አገሮችን ነው፤ ወሃው ከደለል ነጻ የሆነና የተመጣጠነ ውሃ ወደ ግርጌ ተፋሰስ አገሮች ስለሚለቀቅላቸው ዋናው አገልገሎቱ ለሱዳንና ለግብጽ ነው
ማጠቃለያ
ከላይ እንደተገለጸው የአባይ ግድብ በዋናነት የሚጠቅመው ሱዳንን እና ግብጽን መሆኑ ግልጽ ነው፤ ምንም ገንዘብ ሳያወጡ በኢትዮጵያውያን ላብ እና ደም የተሰራላቸውን የደለል መቆጣጠሪያ ግድብ እና የመስኖ ልማት የመጠቀም እደሏን እሰከመጨረሻ ያዳፈነ ፐሮጀክት ሊጠሉት የሚችሉበት እና አባይ ግድብን ለማስቆምም ይሁን አደጋ ለማድረስ የሚያስችል ምንም አይነት ነባራዊ ሁኔታዎች የሉም፡ ራሱ ወያኔ ካላፈረሰው በቀር፤ በዚህ ደግሞ የትግሬ ነጻ አውጭ ግንባር ተመክሮ አለው፡ አዲስ አበባ ውስጥ የህዝብ ትራንስፖርት ላይ ፈንጂ ቀብረው ንጹሃን ዜጎችን መጨረሳቸውን ሊዘነጋ አይገባም፡
ስለዚህ ግብጽ ስለ አባይ እንዲህ አለች እንደዛ አለች፡ ሱዳን ይህን አለ የሚባለው ወሬ ሁሉ የወያኔና ግብረ አበሮቹ የተለመደ አኪልዳማ፤ ሃረካት ክፍል መሆኑን መረዳትና ለዚህ ወሬ ትኩረት ሳንሰጥ አገራችንን አገራዊ አመራር እንዲኖራት ማድረጉ ላይ ትኩረት መስጠት አለብን። ስለ አባይ ተፋሰስ ልማት ወደፊት ህዝብ የሚመክርበና የሚወስንበት ጉዳይ ነው፡ ምናልባትም አሁን በመሰራት ላይ ያለው ግድብ ቆሞ ከላይ ላሉት ግድቦች ቅድሚያ ሊሰጥ የሚችልበት አጋጣሚም ሊኖር ይችላል።፡ከሁሉ የሚቀድመው ግን ነጻነት ስለሆነ የትግሬ ነጻ አውጭ ግንባርን ጠባብ ዘረኛ የግዞት ቀንበር መስበር ያስፈልጋል፡ የተጀመረውን ሁለገብ ትግል ማጋጋልና ማጠናከር አለብን አንጂ ስለአባይ ወያኔ የሚያቀብለንን ጉላንጆ በማላመጥ ጊዜም ጉልበትም ማባከን አይገባንም ብዬ ሃሳቤን አጠቃልላለሁ፡
እግዚአብሄር ኢትዮጵያን ይጠብቅ
ኢትዮጵያን ኢትዮጵያዊ አመራር ይስጣት
አመሰግናለሁ
እስከ ነጻነት
Posted by shume worke at 2:34 AM No comments:
Email ThisBlogThis!Share to XShare to FacebookShare to Pinterest

Opposition Protest Could Mark Change in Ethiopian Policy By Peter Heinlein, VOA June 4, 2013


A peaceful protest rally in the Ethiopian capital, Addis Ababa, has sparked speculation the government may be relaxing its tight restrictions on political demonstrations.  The large turnout at the rally has also raised the profile of a little-known opposition party that seems to be attracting a large following among Ethiopia’s disaffected youth.

Sunday’s demonstration drew thousands to the streets of Addis.  But estimates of how many thousands varied widely.  State-run television reported it was 2,000, while organizers said it was more like 15,000 to 20,000.

Whatever the figure, the event was significant.  It marked the first time authorities have allowed a mass political protest in Addis Ababa since 2005, when police gunned down demonstrators who accused the ruling party of fraud in parliamentary elections.

Pictures and video of the demonstration created a sensation on the Internet, prompting speculation about whether Prime Minister Hailemariam Desalegn’s government might be easing restrictions on political speech imposed by his predecessor, the late Meles Zenawi.

It also raised questions about whether a new generation of opposition leaders might be emerging.  The rally was organized by the Semayawi (Blue) Party, a small offshoot of an opposition group that collapsed following the 2005 election.

Party president Yenekal Getinet said the Blue Party represents the desire for change among the 70 percent of Ethiopians under the age of 35, who he said want to break away from the Marxist ideas that have dominated the country’s political thinking for more than a generation.

“This is a new generation of leaders," said Getinet. "Many political leaders for the last 20 years, be it in the ruling party or opposition are from the leftist ideology or Marxist-Leninist mindset and ethnocentric.  So this is the new generation from the globalization era, a bit liberalized, vibrant and knowledge-based; and this may be the reason why, I am from the new generation.”

The protest was mainly called to demand the release of political prisoners, including opposition leaders, journalists and the organizers of last year’s Muslim protests that called for an end to government interference in religious affairs.

Government spokesman Shimeles Kemal was quoted Monday as saying the overwhelming majority of the protestors were Muslims, including Islamic extremists.  But law professor Yakob Hailemariam, who is representing the Muslim protest organizers in court, and was the keynote speaker at Sunday’s rally, said the demonstrators represented a broad spectrum of Ethiopian youth.

"Actually, the number of Muslims was only one-fifth, it was not very significant.  They stand out because of their clothes, but they were not that many.  But the demo was espousing their cause that Muslim jailed leaders should be released, so that was one of the demands, but it has not religious sentiment to it," said Yakob.

Yakob, who is gained prominence as a senior prosecutor with the International Criminal Tribunal for Rwanda, expressed surprise that Ethiopia’s ruling EPRDF party had allowed the demonstration.  He said it is too early to know whether this represents a change in the tight restrictions on protests that have been in effect since the 2005 post-election violence.

"It Is hard to tell.  The EPRDF is secretive and it is difficult to know what their intentions are.  I have been wondering why they allowed this demonstration.  Are they opening up?  Is this an indication?  Because they have been prohibited since 2005.  Strictly prohibited," said he said.

Blue Party leader Getinet declined to speculate about whether authorities would tolerate more protests.

Other opposition figures, including Yakob Hailemariam, have noted that the demonstration permit had been issued just before last month’s African Union summit, when the government’s restrictions on political speech were under scrutiny by a host of international visitors, including U.S. Secretary of State John Kerry.

Yenekal said the test will come in three months, when the Blue Party plans to ask for another demonstration permit to press its demands for release of political prisoners.

Critics allege Ethiopia has become a de facto one-party state, noting the ruling EPRDF’s near total domination of all elections since 2005.  The late prime minister Meles Zenawi rejected that label, however, calling it a dominant-party state.
Posted by shume worke at 2:26 AM No comments:
Email ThisBlogThis!Share to XShare to FacebookShare to Pinterest

Monday, June 3, 2013

ምርመራው ወደ አቃብያነህጉ ተዛወረ!

የሙስናው “ሻርኮች” በዒላማ ውስጥ?
berhane
June 3, 2013 08:40 am By Editor Leave a Comment
* “አዲስ ነገር የለም” ጸረ ሙስና ኮሚሽን
በተለያዩ ከፍተኛ ወንጀሎች በተጠረጠሩ ሰዎች ላይ የተከፈቱ ክሶችን በማፈንና በመመሪያ ፍትህ በማዛባትና በማቋረጥ ወንጀል የተጠረጠሩ አቃቤያነህግ ላይ ምርመራ መጀመሩ ከፍተኛ ድንጋጤ መፍጠሩ ተሰማ። በተለይም ከወንጀል ጋር ቁርኝት እንዳላቸው በህዝብ የሚታወቁ ክፍሎች ክፉኛ መደናገጣቸው ተሰምቷል።
በሙስና የተጠረጠሩት የጉምሩክ ባለስልጣናት፣ ተባባሪ ነጋዴዎችና ደላሎች መታሰራቸውን ተከትሎ ከተፈጠረው ስሜት በላይ ከፍተኛ መደናገጥ የፈጠረው ዜና አዲስ አድማስ ጋዜጣ ቅዳሜ እለት ለንባብ ያበቃው ዜና ነው።
በቅርቡ ከሃላፊነታቸው የተነሱት የፍትህ ሚኒስትር አቶ ብርሀነ ሃይሉና ከአስር በላይ አቃብያነህግ በተለያዩ ጉዳዮች የተመሰረቱ ክሶች እንዲቋረጡ አድርገዋል በሚል ተጠርጥረው መመርመራቸው በትክክል ከተሰራበት ዋንኛ የሚባሉትን የሙስና ወንጀል “ሻርኮች” በቁጥጥር ስር ለማዋል እንደሚያስችል ከፖሊስ ያገኘነው ጥቆማ ያመለክታል።
“የበርካታ ጉዳዮች ክስ እንዲቋረጥ መደረጉን እናውቃለን” በማለት ለጎልጉል ጥቆማ የሰጡት የፖሊስ አባላት “ይህ ጉዳይ ከተነሳና በትክክል ከተሰራበት የማይጎተት የለም” በማለት በትዕዛዝና በመመሪያ የተቋረጡ የምርመራና የክስ ፋይሎች በርካታ መሆናቸውን ያስረዳሉ።
ተቋማትንና ጉዳዮችን ስም በመጥራት መናገር እንደሚቻል የጠቆሙት ክፍሎች እንዲቋረጡ  የተደረጉ የክስ ሂደቶችን አስመልክቶ ህዝብ ነጻ መድረክ ቢሰጠው የተሻለ እንደሆነ አመልክተዋል። የፌደራል የስነ ምግባርና የጸረ ሙስና ኮሚሽን የቅርብ ሰው የሆኑ የጎልጉል ምንጭ በበኩላቸው “ኮሚሽኑ የመረጃና የማስረጃ ችግር የለበትም። በርካታ አቤቱታዎች ቀርበውለታል። ግን ሳይፈቀድለት መራመድ አይችልም” በማለት ማነቆው ከላይ እንደሆነ አስረድተዋል።
አሁን ስለተፈጠረው አዲስ ሂደት ሲያስረዱ “አዲስ ነገር የለም” በማለት ፍትህ ሚኒስትሩንና የፍርድ አስፈጻሚ አካላትን በስልክና በቃል መመሪያ በመስጠት ሲያዙ የነበሩት ክፍሎች አስቀድመው የሚታወቁና ኮሚሽኑ ከቁጥር በላይ መረጃ የሰበሰበበት እንደሆነ አመልክተዋል። ከደህንነቱ ጋር በቁርኝት የሚሰራው ኮሚሽኑ ራሱ ውስጥም ተመሳሳይ መነካካት እንዳለበት ጠቁመዋል። ዝርዝር ጉዳዩን ለመናገር አይቻልም ብለዋል።
አዲስ አድማስ አስር አቃቤ ህጉጋን እንደሚታሰሩ ጠቅሶ የዘገበው ዜና እነሆ
በቅርቡ ከስልጣን የተነሱት የፍትህ ሚኒስትር አቶ ብርሃነ ኃይሉና ከአስር በላይ አቃቤ ህጐች በሙስና፣ በሽብርተኝነትና በግድያ ወንጀል በተጠረጠሩ ግለሰቦች ላይ የተመሰረተን ክስ ያለአግባብ አቋርጠዋል በሚል በፖሊስ ምርመራ እየተካሄደባቸው መሆኑን ምንጮች ገለፁ፡፡ ፖሊስ በሚኒስትሩና በአቃቤ ህጐቹ ቢሮ ባካሄደው ከፍተኛ ብርበራ በርካታ መዝገቦችን ማግኘቱንና ለምርመራ መውሰዱን ምንጮች ተናግረዋል፡፡ በፖሊስ ብርበራ የተገኙት መዝገቦች ያለአግባብ ተቋርጠው እንዲዘጉ የተደረጉ ክሶች ናቸው ተብሏል፡፡
ተከሳሾች ላይ በቂ ማስረጃ ማቅረብ ካልተቻለ ክሶቹን አቋርጦ መዝገቡን መዝጋት የፍትህ ሚኒስትርና የአቃቤ ህጐች ስልጣን መሆኑ ቢታወቅም ከሙስና፣ ከሽብርተኝነትና ከግድያ ጋር የተያያዙት እነዚህ በፖሊስ ብርበራ የተገኙ ከደርዘን በላይ የሆኑ መዝገቦች ግን፣ በቂ ማስረጃ እያለ፣ ያለ አግባብ የተቋረጡ ናቸው ተብሏል፡፡ ምርመራው ተጠናቆ እንዳበቃ በሚኒስትሩና በአቃቤ ህጐቹ ላይ ክስ እንደሚመሰረትም ምንጮች ጠቁመዋል። ለሰራተኞች አቤቱታ ምላሽ ባለመስጠትና በሥራ ድልድል በደል ፈጽመዋል በሚል ቅሬታ ይቀርብባቸው የነበሩት የፍትህ ሚኒስትሩ፤ በተለይ የጥብቅና ፈቃድ አሰጣጥ ላይ ይታያሉ የተባሉ ችግሮችን እንዲፈቱ አራት የማሳሰቢያ ደብዳቤዎች ተጽፎላቸው እንደነበር ምንጮች ገልፀዋል፡፡ በሚኒስትሩ ላይ ከባለጉዳዮችም የተለያዩ ቅሬታዎች ይሰነዘሩ ነበር ያሉት ምንጮች፤ የታራሚዎች የይቅርታ ጥያቄን ማዘግየትና ተገቢ ምላሸ አለመስጠት በዋናነት እንደሚጠቀስ ገልፀዋል፡፡
በቅርቡ በተካሄደው የኢህአዴግ ዘጠነኛ ጉባኤ ላይ ከፓርቲው መሪዎችና አባላት ለሚኒስትሩ የቃል ማሳሰቢያ ተሰጥቷቸው እንደነበር ምንጮች ገልፀው፣ ፓርላማም የመ/ቤቱ በርካታ ችግሮች መፈታት እንዳለባቸው ማሳሰቡ ይታወሳል፡፡ በኢህአዴግ ዘጠነኛ ጉባኤ ላይ የአገሪቱ ዋና ችግር በከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ላይ የሚታይ እንደሆነ መገለፁ ይታወቃል፡፡ በዚህ ዓመት ብቻ ሶስት ሚኒስትሮች በወንጀል ተጠርጥረው ከስልጣን የወረዱ ሲሆን፣ የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትር የነበሩት አቶ ጁነዲን ሳዶ ከአገር መኮብለላቸው ይታወሳል፡፡ (ፎቶ አዲስ አድማስ)
Posted by shume worke at 1:23 PM No comments:
Email ThisBlogThis!Share to XShare to FacebookShare to Pinterest

Sunday, June 2, 2013

Thousands march for rights in rare Ethiopia protest

Reuters) - About 10,000 Ethiopians staged an anti-government procession on Sunday in the first large-scale protest since a disputed 2005 election ended in street violence that killed 200 people.
The demonstrators marched through Addis Ababa's northern Arat Kilo and Piazza districts before gathering at Churchill Avenue in front of a looming obelisk with a giant red star perched on top, a relic of Ethiopia's violent Communist past.
Some carried banners reading "Justice! Justice! Justice!" and some bore pictures of imprisoned opposition figures. Others chanted, "We call for respect of the constitution".
A few police officers watched the demonstration, for which the authorities had granted permission.
"We have repeatedly asked the government to release political leaders, journalists and those who asked the government not to intervene in religious affairs," said Yilekal Getachew, chairman of the Semayawi (Blue) Party which organized the protests.
He said the demonstrators also wanted action to tackle unemployment, inflation and corruption.
"If these questions are not resolved and no progress is made in the next three months, we will organize more protests. It is the beginning of our struggle," he told Reuters.
Government officials were not immediately available for comment.
ANTI-TERRORISM LAW
Ethiopian opposition parties routinely accuse the government of harassment and say their candidates are often intimidated in polls. The 547-seat legislature has only one opposition member.
Though its economy is one of the fastest-growing in Africa, Ethiopia is often criticized by human rights watchdogs for clamping down on opposition and the media on national security grounds, a charge the government denies.
Critics point to a 2009 anti-terrorism law that makes anyone caught publishing information that could induce readers into acts of terrorism liable to jail terms of 10 to 20 years.
Last year, an Ethiopian court handed sentences of eight years to life to 20 journalists, opposition figures and others for conspiring with rebels to topple the government.
More than 10 journalists have been charged under the anti-terrorism law, according to the Committee to Protect Journalists, which says Ethiopia has the highest number of exiled journalists in the world.
Muslims, who form about a third of Ethiopia's mostly Christian population, staged mosque sit-ins in 2012, accusing the government of meddling in religious affairs and jailing their leaders.
Ethiopia, long seen by the West as a bulwark against radical Islamists in neighboring Somalia, denies interfering, but says it fears militant Islam is taking root in the country.
(Reporting by Aaron Maasho; Editing by George Obulutsa and Alistair Lyon)
Posted by shume worke at 12:35 PM No comments:
Email ThisBlogThis!Share to XShare to FacebookShare to Pinterest

ሰላማዊ ሰልፉ በሰለም ተጠናቀቀ፡፡

June 2, 2013 | Filed under: News | Posted by: admin
944521_502719046450298_831415286_nሰላማዊ ሰልፉ በሰለም ተጠናቀቀ፡፡
መንግስት በ3 ወር ውስጥ ጥያቄያችንን ካልመለስ በተጠናከረ መልኩ ድምፃችንን እናሰማለን! (ሰማያዊ ፓርቲ)
ያለ አግባብ የታሰሩ የፖለቲካ የሀይማኖት እና የህሊና እስረኞች እንዲፈቱ፤ ከቀዬአቸው የተፈናቀሉ ዜጎች በአግባቡ እንዲመለሱ እና አፈናቃዮች ለፍርድ እንዲቀርቡ፤ የኑሮ ውድነቱ አስተማማኝ እልባት እንዲሰጠው እና ሌሎችንም ጥያቄዎች አንግበው ዛሬ ኩባ አደባባይ የተገናኙት ኢትዮጵያውን ሰላማዊ ሰልፋቸውን በሰላም አጠናቀቁ!
ሰልፉ ከጠዋቱ አራት ሰዓት ጀምሮ እስከ ስምንት ሰዓት ድረስ እጅግ ደማቅ በሆነ መልኩ የተከናወነ ሲሆን ቀበና ከሚገኘው ሰማያዊ ፓርቲ ፅ/ቤት አንስቶ በአራት ኪሎ በፒያሳ እና በቸርቸር ጎዳና ሄዶ መድረሻውን ኩባ አደባባይ አድርጓል፡፡
ሰማያዊ ፓርቲ በሰልፉ ላይ መንግስት በ3 ወር ጥያቄያችንን ካልመለሰ በተጠናከረ መልኩ ድምፃችንን እናሰማለን ብሏል፡፡
ሰልፉ በሰላም በመጠናቀቁ የተሰማኝን ደስታ በዚህ አአጋጣሚ እገልፃለሁ በሌላ አጋጣሚም እደግመዋለሁ!
Posted by shume worke at 8:02 AM No comments:
Email ThisBlogThis!Share to XShare to FacebookShare to Pinterest

አዲስ አበባ በሰላማዊ ሰልፍ ደምቃ ዋለች!


Flickr logo. If you click it, you'll go home
  • Sign Up
  • Explore
  • Upload
  • Sign In

Semayawi party demonstration 2013

ECADF Ethiopian News

Addis Ababa Semayawi party demonstration June 01, 2013

36

Photos

214

Views

  • View all sets
  • Photos
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
ECADF Ethiopian News
[★]
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
ECADF Ethiopian News
[★]
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
ECADF Ethiopian News
[★]
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
ECADF Ethiopian News
[★]
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
ECADF Ethiopian News
[★]
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
ECADF Ethiopian News
[★]
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
ECADF Ethiopian News
[★]
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
ECADF Ethiopian News
[★]
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
ECADF Ethiopian News
[★]
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
ECADF Ethiopian News
[★]
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
ECADF Ethiopian News
[★]
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
ECADF Ethiopian News
[★]
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
ECADF Ethiopian News
[★]
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
ECADF Ethiopian News
[★]
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
ECADF Ethiopian News
[★]
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
ECADF Ethiopian News
[★]
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
ECADF Ethiopian News
[★]
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
ECADF Ethiopian News
[★]
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
ECADF Ethiopian News
[★]
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
ECADF Ethiopian News
[★]
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
ECADF Ethiopian News
[★]
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
ECADF Ethiopian News
[★]
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
ECADF Ethiopian News
[★]
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
ECADF Ethiopian News
[★]
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
ECADF Ethiopian News
[★]
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
ECADF Ethiopian News
[★]
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
ECADF Ethiopian News
[★]
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
ECADF Ethiopian News
[★]
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
ECADF Ethiopian News
[★]
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
ECADF Ethiopian News
[★]
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
ECADF Ethiopian News
[★]
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
ECADF Ethiopian News
[★]
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
ECADF Ethiopian News
[★]
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
ECADF Ethiopian News
[★]
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
ECADF Ethiopian News
[★]
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
Addis Ababa Semayawi party demonstration June 2, 2013
ECADF Ethiopian News
[★]
  • Square
  • Small
  • Medium

◣
Guide

  • Português
  • Tiahoo!. All rights reserved.
  • Posted by shume worke at 6:15 AM No comments:
    Email ThisBlogThis!Share to XShare to FacebookShare to Pinterest
    Newer Posts Older Posts Home
    Subscribe to: Posts (Atom)

    Blog Archive

    • ▼  2013 (53)
      • ►  October (4)
      • ►  September (5)
      • ►  August (3)
      • ►  July (2)
      • ▼  June (8)
        • የኢትዮጵያ የአበባ ምርት በአፍጋኒስታን ገበያ አገኘ እንዴ?
        • ይድረስ,,,,ለአጼ ቴዎድሮስ
        • የሰሞኑ የአባይ ግርግር
        • Opposition Protest Could Mark Change in Ethiopian ...
        • ምርመራው ወደ አቃብያነህጉ ተዛወረ!
        • Thousands march for rights in rare Ethiopia protest
        • ሰላማዊ ሰልፉ በሰለም ተጠናቀቀ፡፡
        • አዲስ አበባ በሰላማዊ ሰልፍ ደምቃ ዋለች!
      • ►  May (3)
      • ►  April (2)
      • ►  March (8)
      • ►  February (6)
      • ►  January (12)

    About Me

    My photo
    shume worke
    View my complete profile
    Watermark theme. Powered by Blogger.