Thursday, September 26, 2013

አንድነት የገጠመው ሳንክና የሰልፉ ዝግጅት

የአንድነት ለዲሞክራሲ እና ፍትህ ፓርቲ የፊታችን እሁድ በአዲስ ኣበባ ከተማ ለማካሄድ የጠራውን ሰላማዊ ሰልፍ ለማጨናገፍ መንግሥት ከወዲሁ እየተንቀሳቀሰ ቢሆንም ሰልፉን ግን ከማካሄድ ወደኃላ እንደማይል የፓርቲው ሊቀመንበር ዶ/ርነጋሶ ጊዳዳ አስታወቁ ።
ዶ/ር ነጋሶ
ትላንት ለተወሰነ ጊዜ በጉለሌ ፖሊስ ጣቢያ መታሰራቸውንም አረጋግጠው ነገር ግን ያደረሱብን እንግልት የለም ብለዋል የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳ ዳ ዛሬ
ለዶቸቬሌ እንደገለጹት ፓርቲያቸው ኣንድነት ለዲሞክራሲ እና ፍትህ ለፊታችን እሁድ
በአዲስ ኣበባ ከተማ ታላቅ ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ ጠርተዋል በዚሁመሰረት
የተቀናጀ የቅስቀሳ ስራም ተጀምረዋል ቅስቀሳውደግሞ የኣንድነት ለዲሞክራሲ
እና ፍትህ ፓርቲ ሊቀመንበሩ ዶ/ርነጋሶ ጊዳዳ እንደገለጹት ሶስት ኣይነት
መልክ ያለው ነው አንደኛው የፓርቲው አባላት አስራ አምስት እራሳቸውን እየሆኑ በተከራዩ
ሚኒባስ ተሽከርካሪዎች ኣማካንነት በየክፍለ ከተማው እየተዘዋወሩ በራሪ ወረቀቶችን
እንዲበትኑ ሁለተኛው በእነዚህ ተሽከርካሪዎች ላይ የጥሪ ፓስተሮች እንዲለጠፉ ማድረግ
እና ሶስተናው በደግሞ ድምጽ ማጉያዎች ኣማካይነት ከተሽከርካሪዎቹ ላይ
ጥሪውን ማስተጋባት ናቸው በዚሁ መሰረት ቅስቀሳው ተጀምሮ ሳለ ዶ/ር ነጋሶ እንደሚሉት
ከትላንት በስትያ ማክሰኖ ነበር ችግሮች ማጋጠም የጀመሩት
የኣንድነት ፓርቲ ኣመራር በችግሩ ላይ ከመከረ በኋላ ዶ/ር ነጋሶ እንደገለጹት አባላቱ
በሚታሰሩበት ስፍራ ዓመራሩም እየተከተለ ከተቻለ ለማስፈታት ካልሆነም እነሱን ኣስወጥቶ
ለመታሰር እና ይህም ካልተቻለ አብሮ ለመታሰር ውሳኔ ኣስተላልፈዋል በትላንትናው እለትም
እንደዚሁ ወደ ኮልፌ ሽሮሜዳ እና ንፋስስልክ ኣቅጣጫዎች ሶስትየቅስቀሳ ቡድን እንደተሰማራ
ወዲያውኑ እስራት ተጀመረ ዓመራሩም በውሳኔው መሰረት ተከትሎ ይሄዳል ዶ/ር ነጋሶም በዚሁ
መሰረት ነበር ወደ ሽሮሜዳ ያቀኑት
ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ እንደሚሉት ደግሞ የአዲስ ኣበባ ኣስተዳደር በነጋሪትጋዜጣ
ባይታወጅም ውስጥ ውስጡን እንደ መመሪያ የሚተላለፍ ደምብ ኣውጥተዋል
እንደ ሰልፉ ሁሉ ለማንናውም የቅስቀሳ ስራም ፈቃድ ያስፈልጋል የሚል
ታግተው በቆዩባቸው ሳዓታት የደረሰባቸው አካላዊም ሆነ ስነልቦናዊ በደልካለ
ዶ/ርነጋሶንጠይቄኣቸውነበር
በጉዳዩ ላይ የበኩላቸውን ምላሽ እንዲሰጡ በአዲስኣበባ ፖሊስ ኮሚሺን ወደጉለሌክ/ከተማ
የፖሊስ መምሪያደውዬነበር ነገርግንስልኩንያነሱትግለሰብ ሌላው ቀርቶ ስማቸውንም ሆነ
ማዕረጋቸውን ለመግለጽ ካለመፈለጋቸውም በላይ ዶ/ርነጋሶ በጭራሽ ወደጣቢያውኣልመጡም
የምናውቀው ነገር የለም በማለት ነበር ስልኩን የዘጉት

ወታደራዊ መኮንኖች የደሞዝ ይጨመርልን ጥያቄ አቀረቡ

መስከረም ፲፭(አስራ አምስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖች ካለፉት 8 ቀናት ጀምሮ ስብሰባ ላይ ሲሆኑ የደሞዝ ጭማሪ ጥያቄ ዋነኛው የመነጋገሪያ አጀንዳ መሆኑ ታውቋል።
ከመቶ አለቃ በላይ ማእረግ ያላቸው ወታደራዊ መኮንኖች ስብሰባዎችን እያካሄዱ ያሉት የጄኔራሎች ስብሰባ ከወር በፊት መጠናቀቁን ተከትሎ ነው። በጄኔራሎቹ ስብሰባ ላይ ለሰራዊቱ የደሞዝ ጭማሪ ጥያቄ ተነስቶ የነበረ ቢሆንም፣ “ሰራዊቱ አሁን የሚያገኘው ደሞዝ ለኑሮው በቂ ነው” የሚል መልስ ከሰራዊቱ ዋና አዛዦች ተሰጥቷል።  በተሰጠው መልስ የተበሳጩት  ጄኔራል ሰአረ መኮንን ስብሰባ ረግጠው ወጥተው እንደነበር ታውቋል። ጄኔራሉን ለማረጋጋት ከፍተኛ ጥረት ተደርጎ እንደነበርም የደረሰን መረጃ ያመለክታል። ጄኔራል ሰአረ ለሰራዊቱ ደሞዝ እንዲጨመር አቋም ከያዙት ከፍተኛ መኮንኖች መካከል አንዱ ናቸው።
ሰሞኑን በመካሄድ ላይ ባለው ከጄኔራል በታች ማእረግ ባላቸው መኮንኖች ስብሰባም   የደሞዝ ጭማሪና የኑሮ ውድነት ዋና አጅንዳ ሆኖ ቀርቧል።
በምስራቅ አካባቢ ባለው እዝ አንዳንድ መኮንኖች ” እኛ ቤተሰቦቻችንን ምግብ አብልተን ለማኖር አልቻልንም፣ እናንተ በሙስና በዘረፋችሁት ገንዘብ ልጆቻችሁን ውጭ አገር ልካችሁ ታስተምራላችሁ” በሚል አለቆቻቸውን በድፍረት መተቸታቸውን የውስጥ ምንጮች ገልጸዋል።   መኮንኖች ያቀረቡትን ጥያቄ የመደረክ መሪዎች ለመመለስ ሲቸገሩ ታይቷል።
መኮንኖቹ ስብሰባቸውን ሲጨርሱ ከተራ ወታደሮች ጋር የሚደረገው ስብሰባ ይቀጥላል ተብሎአል።
ከፍተኛ ቅሬታ እየተስተናገደበት ባለው ስብሰባ፣ ወታደሮቹ እንደ መኮንኖቹ ሁሉ የደሞዝ ጭማሪ ጥያቄ ሊያነሱ ይችላሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ወታደራዊ ምንጮች ገልጸዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ አንድ ሻምበል የወለደውን ልጅ በእሳት ማቃጠሉ ታውቋል። በምስራቅ እዝ የሚገኘው ሻምበል ፈቃዱ በዳዳ ከሳምንታት በፊት በልጁ ላይ ቤንዜን በማርከፍከፍ ያቃጠለው ሲሆን፣ ልጁም ወዲያውኑ ህይወቱ ሲያልፍ አባቱ ደግሞ ቆስሎ ሆስፒታል ተኝቷል። ሻምበል ፈቃዱ በልጁ ላይ ይህን አሰቃቂ እርምጃ ለምን እንደወሰደ አልታወቀም።

Wednesday, September 18, 2013

የቤተመንግስት ደህንነት ሃላፊ ተነሱ (ከኢየሩሳሌም አርአያ)

የቤተ-መንግስት የደህንነት ጥበቃ ዋና ሃላፊ ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩት የሕወሐት አባል አቶ ጌታቸው ተፈሪ ከስልጣናቸው መነሳታቸውን ምንጮች አስታወቁ። አቶ ጌታቸው ቀደም ሲል በክልል 14 ፖሊስ ኮሚሽን የደሕንነት ልዩ ተወርዋሪ ሃይል ሃላፊ ተደርገው ሲያገለግሉ መቆየታቸውን የጠቆሙት ምንጮች፣ ከዚያም ወደ ቤተ መንግስት ተዛውረው መመደባቸውንና በተጨማሪ የአገር ውስጥ ደህንነት ምክትል ሃላፊ በመሆን ከአቶ ወ/ስላሴ ወ/ሚካኤል ጋር ሲሰሩ መቆየታቸውን አስረድተዋል። የአቶ መለስና ወ/ሮ አዜብ የቅርብ ሰው የሆኑት አቶ ጌታቸው ተፈሪ በነበራቸው ታማኝነት የቤተመንግስት የደህንነት ሃላፊ ተደርገው በአቶ መለስ ተመርጠው እንደተሾሙ ያስታወሱት ምንጮች፣ በማያያዝም እስከ 1994ዓ.ም የቤተመንግስት የደህንነት ጥበቃ በሃላፊነት ሲመሩ የቆዩት አቶ ዘርኡ መለስ በወቅቱ ከአቶ መለስ ጋር በፈጠሩት የፖለቲካ ልይነት ምክንያት ካዛንቺስ አካባቢ በሚገኘው የቀድሞ “ኮከብ ሬስቶራንት” የአሁኑ “ሚልክ ሃውስ” መኖሪያ ሕንፃ አንደኛ ፎቅ ቤታቸው ውስጥ አንገታቸው በስለት ታርዶና በድናቸው ተበላሽቶ መገኘቱን አመልክተዋል። ይህን አሰቃቂ ግድያ ያከናወነው አሁን በእስር ቤት የሚገኘው የቀድሞ አገር ውስጥ ደህንነት ሃላፊና የአቶ መለስ ቀኝ እጅ ወ/ስላሴ ወ/ሚካኤል መሆኑን ምንጮቹ አጋልጠዋል።
አቶ ጌታቸው ተፈሪ ከስልጣን እንዲነሱ የተደረገው በደህንነት ዋና ሹም አቶ ጌታቸው አሰፋ ትእዛዝ መሆኑን ያመለከቱት ምንጮች፣ በአሁኑ ወቅት በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ እንደማይታወቅ ጠቁመዋል። አቶ ጌታቸው ተፈሪ የወ/ስላሴ መታሰር ቅር ሳያሰኛቸው እንዳልቀረና በተጨማሪም የነአዜብ ቡድን ደጋፊ መሆናቸውን ምንጮቹ

Monday, September 2, 2013

በመንግስታዊ ውንብድና ትግላችን አይገታም! ሰማያዊ ፓርቲ

ከሰማያዊ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ
ሰማያዊ ፓርቲ ግንቦት 25 ቀን 2005 ዓ.ም. ባካሄደው ታላቅ ሕዝባዊ የተቃውሞ ሰልፍ ለመንግሥት ያቀረባቸው ጥያቄዎች አስፈላጊው ምላሽ እንዲሰጣቸው በመጠየቅ ይህ ካልሆነ ግን ከሦስት ወር በኋላ ተቃዉሞውን ከፍ ባለ ደረጃ እንደሚያቀርብ በመጋለፅ ሰልፉን አጠናቋል፡፡ ለተነሱት ጥያቄዎች የተገኘ ምላሽ ባለመኖሩ ፓርቲው ለሕዝብ በገባዉ ቃል መሠረት ነሐሴ 26 ቀን 2005 ዓ.ም. ታላቅ የተቃዉም ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሔድ በመወሰን በሕግም ሆነ በሥራ የሚያስፈልጉ ነገሮችን በማጠናቀቅ እለቱን በመጠበቅ ላይ እያለ ምንም አይነት መለዮ ባልለበሱ ግለሰቦች የሚመራ የፖሊስ መለዮ ለባሽ ታጣቂዎች ከሕግ ውጭ ነሐሴ 25 ቀን 2005 ዓ.ም. ከምሽቱ 12 ሰዓት አካባቢ የፓርቲውን ቢሮ ጥሰው በመግባት ፓርቲው ይጠቀምባቸው የነበሩ የቅስቀሳ ቁሳቁሶችና ሌሎች የፓርቲውን ንብረቶች ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ ወርሰዋል፡፡ በፓርቲው ፅ/ቤት የነበሩ አባላትን እና መሪዎችን በጠመንጃ በማስገደድ ወደተለያዩ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጣቢያዎች ከፋፍሎ በመውሰድ አስረዋል፣ ዘልፈዋል፣ አስፈራርተዋል እንዲሁም አረመኔያዊ በሆነ መንገድ ደብድበዋል፡፡ አንዳንዶችን በጭቃ ላይ ጭምር አንከባለዋል፡፡ ይህ ሁሉ ሕገ ወጥና አረመኔያዊ ድርጊት ሕገ መንግስታዊ የሆነውን መብታቸውን በሚጠቀሙ ዜጎች ላይ ሲፈፀምና በሕግ ማስከበር ስም በቁጥጥር ሥር በዋሉ ዜጎች ላይ የግል ጥላቻን መወጣጫ እስኪመስል ድረስ ማንኛዉንም የማንአለብኝነት ድርጊት ሲፈፅሙ ማየት ያልታጠቁ ዜጎችን አቅመ ቢስነትና የሕግ ከለላ ማጣትን ገሃድ አድርጎታል፡፡ ይሕ አይነቱ የጡንቻ ሥራ በአንድ በኩል ልብን በሐዘን የሚሰብር ድርጊት ሲሆን በሌላ በኩል ለነፃነትና ለፍትህ የሚደረገው ትግል እጅግ ትክክለኛና ወቅታዊ መሆኑን ያረጋግጣል፡፡
ሰማያዊ ፓርቲ የሚያደርጋቸው እንቅስቃሴዎች ሕጋዊ እንዲሆኑ አስፈላጊውን ሁሉ አድረጓል፡፡ የአስፈፃሚው አካላት በሕግ ከተሰጣቸው ስልጣንና ተግባር በመውጣት የፈለጉትን ለማድረግ መብት እንደሌላቸው ማሳዬት ፓርቲያችን ከተመሰረተባቸው አብይ መርሆች አንዱ በመሆኑ፤
1ኛ. በአዲስ አበባ ከተማ ከቤት ውጭ የሚደረጉ ስብሰባንና ሰላማዊ ሰልፍን አስመልክቶ ጥያቄዎችን ተቀብሎ በሕግ በተወሰነው መሰረት አስፈላጊውን ሁሉ ማከናወን የሚገባው በአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት የሕዝባዊ ስብሰባና የሰላማዊ ሰልፍ ማሳወቂያ ክፍል ኃላፊነቱን ባለመወጣቱ በፓርቲው ላይ ለደረሰው የአካል፣ የንብረትና የሞራል ጉዳት ምክንያት በመሆኑ በሕግ እንጠይቃለን፤
2ኛ. የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የፓርቲ መሪዎችን በማስፈራራት ከሰልፍ ለማስቀረት የሚያደርገው ድርጊት ከህግ ውጭ በመሆኑና በፖሊስ መለዮ ለባሾች ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ የፓርቲውን ቢሮ በመውረር ለፈፀሙት የንብረት ዘረፋና ውድመት እንዲሁም ፓርቲው ባቀደውና በተዘጋጀበት ጊዜ የተቃውሞ ሰልፉን እንዳያካሂድ በማደናቀፉ በሕግ እንጠይቃለን፤
3ኛ. በሐገራችን ፓርቲዎችን እንዲያስተዳድርና እንዲከታተል ስልጣን የተሰጠው ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እውቅና ሰጥቷቸው በሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች ላይ እንዲህ አይነት ሕገ ወጥ ድርጊት እየተፈፀመባቸው መሆኑን እንዲያውቀው እናደርጋለን፤
4ኛ. የፖለቲካ ትግላችንን በመቀጠል ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብታችንን የትኛውም የአስፈፃሚ አካል የመከልከል መብት ስለሌለው የተቃውሞ ሰልፈችንን ቅዳሜ ጳጉሜ 2 ቀን 2005 ዓ.ም በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ እንደምናከናውን ለአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት የሕዝባዊ ስብሰባና የሰላማዊ ሰልፍ ማሳወቂያ ክፍል በዛሬው ዕለት አሳውቀናል፡፡
በመሆኑም ከዚህ ቀደም ለመንግስት ያቀረብናቸው ጥያቄዎች እንደተጠበቁ ሆነው በተደጋጋሚ እንዳስተዋልነው በዚህች ታሪካዊት ሐገር የሕግ የበላይነት ግብዓተ መሬት ከመፈፀሙ በፊት እንድንደርስላት ለዘመቻ የሕግ የበላይነት ትግላችን የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪክ ማሕበራትና ዜጉች በአጠቃላይ ከጎናችን እንዲሰለፉ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡
በመንግስታዊ ውንብድና ትግላችን አይገታም!!!!
ነሐሴ 27 ቀን 2005 ዓ.ም.
አዲስ አበባ

Sunday, September 1, 2013

Terror on The Blue Party of Ethiopia

Share
Facebook_eth_picSaturday August 31, 2013 on the eve of the Blue Party called rally in Addis the Blue Party Head Office was attacked by Western financed and supported thugs of the Ethiopian brutal security forces  where more than one hundred members and supporters of the Blue Party was taken to  local prisons beaten up savagely according to Eng Yelekal Getenet the party president.
The regime security thugs unleashed similar beating on fellow Ethiopian Muslims on the Eid al-fiter Celebration this month. The regime believes such brutal beating of women, children, elderly and the young will deter people not to join any peaceful protest any where in Ethiopia.
The regime organized rally in Addis Ababa billed as a rally to fight “Extremists”  tomorrow is a rally to denounce the Ethiopian Muslims for their more than 18 months old struggle for religious freedom. Another target of this “No Food” if you do not come  rally is the Blue Party/Semayawi which is the first party in Ethiopia that stood with the Ethiopian Muslims by taking their call as its call for which it was denounced by Hailemariam Desalegne in public.
The Blue Party of Ethiopia leadership according to the interview Eng. Yelekal Getenet gave on ECADF paltalk  room today its  party head quarter is now under thugs control and he is not sure if they can ever assemble there.
The hundreds thousands supporters and members of the party we all saw three months ago in Addis should turn the regime rally in to opposition rallytomorrow. The Ethiopian Muslim activist had made it clear that they will be doing that.
The Blue Party leadership is not in any position to contact its supporters before tomorrow’s rally therefore it is up to activists to coordinate a successful counter rally.
“Talaku Rucha”, The Great Run in the past had been used by activists as a protest platform. We should not let the regime “Hode Ader” supporters to  endorse the regime killing, Jailing in thousands and beating of Ethiopian Muslims this month alone and  today  more than one hundred  Blue Party members and supporters.
Let Addis Ababeans come out in huge numbers and denounce the regime led by Hailemariam Desalegne for  its brutality and terror. The Extremist in Ethiopia is the regime itself. Peaceful opposition like the Blue Party if it is allowed to be destroyed by terror no other peaceful opposition will ever exist in Ethiopia.
Religious establishments who are bought by the regime should be condemned by all of us because they are  serving humanely “Gods” not the God of their books. Like fellow Ethiopian Muslims the Christians in Ethiopia should be courageous to say no to the religious cadres in their religious institutions.
The Blue Party/Semayawi of Ethiopia is the peoples party and no matter how many of its members and supporters are beaten up or jailed the struggle will continue until the unelected, corrupt and terrorist regime of Ethiopia is removed from powe